የጉጂ ኦሮሞ ብሄረሰብ የአዲባና የጋብቻ ስነ-ስረአት በትውፊታዊ ተውኔት እሳቤ አስረጂነት
Files
Date
2022-06-22
Authors
Journal Title
Journal ISSN
Volume Title
Publisher
Wolkite University
Abstract
ይህ ጥናታዊ ፅሁፍ በዋናነት የሚያተኩረው የጉጂ ኦሮሞ ብሄረሰብ አዲባና የጋብቻ ስነስረአት
በትውፊታዊ ተውኔት እሳቤ አስረጂነት ላይ ሲሆን የአዲባና የጋብቻ ስነ-ስረአት በትውፊታዊ
ተውኔት ውስጥ የሚዳስስ እና የሚተነትን ጥናታዊ ፅሁፍ ነው ። አጥኚው ጥናቱን ለማጥናት
የተጠቀመው የጥናት አይነት ገላጭ የምርምር ዘዴ ሲሆን መረጃ ለመሰብሰብ የተጠቀመባቸው
ዘዴዎችም ቃለ መጠይቅ እና ምልከታ ናቸው ። ስለ አዲባና የጋብቻ ስነ-ስረአት እውቀት ያላቸውን
ሰዎች ቃለ መጠይቅ በማድረግ እና የአጥኚውን ምልከታ ተጠቅሟል ። እንዲሁም ስለ ትውፊታዊ
ተውኔት የተፃፉ መፅሀፍትን እና ጥናታዊ ፅሁፎችን በመዳሰስ ጥናቱ ተጠንቷል።